2012-2017 ዓ.ም ሙሉ ማህበራዊ-ኢኮኖሚያዊ መረጃ
ወራቤ ከተማ በአጭር ጊዜ ውስጥ ዘመናዊ፣ ተደራሽ አገልግሎት ያላት፣ ኢንቨስትመንት የሚስብ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ የኑሮ ሁኔታ ያላት ከተማ ለመሆን።
የከተማውን ማህበራዊ-ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማረጋገጥ ትክክለኛ፣ ወቅታዊ እና ተመጣጣኝ መረጃ በመሰብሰብ፣ በመተንተን እና በማሰራጨት ለእቅድ አውጪዎች፣ ለወሳኝ አካላት እና ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት።
ያሲን ከሊል
ከ1958 ዓ.ም በፊት ወራቤ ትንሽ መንደርና የገጠር ከተማ የነበረች ሲሆን ምንም ዓይነት ማህበራዊ ተቋማት ያልነበሯትና በመንደሯም ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ቁጥር በጣም ጥቂት እንደነበር የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ይጠቁማሉ። በመሆኑም የአካባቢው ነዋሪ ለትምህርት፣ ለጤናና አስተዳደራዊ ነክ ጉዳዮች ቡታጅራና ዝዋይ ከተሞች ይመላለስ እንደነበር ማወቅ ይቻላል። ሆኖም በ1958 ዓ.ም ቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ለአጭር ጊዜም ቢሆን ወራቤን የመጎብኘት እድል ገጥሟቸው ነበር።
ወራቤ የስልጤ ዞን ዋና ከተማ የሆነችው፡- ሚያዚያ 23 ቀን 1993 ዓ.ም በተደረገው የስልጤ ብሔረሰብ የማንነት ህዝበ ውሳኔ ተከትሎ ነው። ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ በከተማ አስተዳደርነት ደረጃ መተዳደር ከጀመረች ጊዜ ጀምሮ በፈጣን እድገት ውስጥ ከሚገኙ የአገራችን ከተሞች አንዷ ሆናለች።
የወራቤ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተ ደቡብ ምዕራብ 172 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኝ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ እስከ ጅንካ የተዘረጋው አስፋልት አቋርጧት የሚያልፍ መሆኑ ለከተማዋ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። በሰሜን ቅቤት፣ በደቡብና ደቡብ ምስራቅ ሁልባረግ፣ በምስራቅ ዳሎቻ፣ በምዕራብ አሊቾ ውሪሮ ጋር ትዋሰናለች።
ምስል 1፡ የወራቤ ከተማ አስተዳደራዊ ካርታ
የወራቤ ከተማ በደቡብ ኢትዮጵያ 8° ላቲቲዩድ እና 38° ሎንግቲዩድ ከባህር ጠለል በላይ ከ2080-2100 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኝ ሲሆን ከዚህ ውስጥ አብዛኛው ሜዳማ መልክዓ-ምድራዊ ገጽታ ሲኖረው የተቀረው ተራራማና ገደላገደል ገጽታ አለው። ከተማዋን የሚያቋርጡ ዲጆና ልማዛ ወንዞች ይገኙባታል። የዝናብ መጠኗም እስከ 1200 ሚ.ሜ ሲሆን የሙቀት መጠንዋ ከፍተኛው 22°C ዝቅተኛው 15°C ነው። የአየር ጸባይዋም ወይና ደጋ የአየር ጸባይ ካላቸው ይመደባል።
የአየር ጸባይ፡ ወይና ደጋ | ዋና ወንዞች፡ ዲጆ፣ ልማዛ፣ ዘይወቴ
ከዚህ በታች የወራቤ ከተማ 10 ቀበሌዎች ካርታዎች ቀርበዋል። እያንዳንዱ ካርታ የቀበሌውን ድንበር እና አቀማመጥ ያሳያል።
የከተማዋ ነዋሪ ብዛት ከ2012 እስከ 2017 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ እድገት አሳይቷል፡፡ በ2012 ዓ.ም 84,512 የነበረው ህዝብ ብዛት በ2013 ዓ.ም 87,574፣ በ2014 ዓ.ም 91,602፣ በ2015 ዓ.ም 97,276፣ በ2016 ዓ.ም 101,945 እና በ2017 ዓ.ም 106,839 ደርሷል፡፡ በ2017 ዓ.ም ከጠቅላላው ህዝብ ብዛት ውስጥ ወንድ 51,865 እና ሴት 54,974 ናቸው፡፡ በከተማዋ የተለያዮ ብሄር ብሄረሰቦች የሚገኙ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የስልጤ፣ የሀድያና የጉራጌ ብሄረሰቦች በብዛት ይገኛሉ፡፡ ስልጥኛና አማርኛ በከተማው በስፋት የሚነገሩ ቋንቋዎች ሲሆኑ ስልጥኛ እና አማርኛ የስራ ቋንቋ ናቸዉ፡፡ በአምስት ዓመታት ውስጥ የህዝብ ብዛት በ22,327 (26.4%) አድጓል፡፡
POPULATION SIZE BY SEX, KEBELE AND YEAR BASED ON 1999 CSA CENSUS DATA - WORABE TOWN ADMINISTRATION 2012-2017 E.C
| YEAR | S.NO | NAME OF KEBELE | MALE | FEMALE | TOTAL |
|---|---|---|---|---|---|
| 2012 | 1 | WERABE TOWN 01+02 | 14,105 | 13,772 | 27,877 |
| 2012 | 2 | ALKESO TOWN | 910 | 899 | 1,809 |
| 2012 | 3 | ARAT BER | 5,326 | 5,639 | 10,965 |
| 2012 | 4 | ANSHOBESO | 5,624 | 5,964 | 11,588 |
| 2012 | 5 | AGEDELE ANSHOBESO | 1,048 | 1,080 | 2,128 |
| 2012 | 6 | DILEDATE | 712 | 756 | 1,468 |
| 2012 | 7 | GERMAMA GALE | 2,709 | 2,845 | 5,554 |
| 2012 | 8 | DATE WEZIR 6 | 4,219 | 4,537 | 8,756 |
| 2012 | 9 | FUGIE ACHERAE | 4,397 | 4,895 | 9,292 |
| 2012 | 10 | ALBAZER | 2,410 | 2,666 | 5,076 |
| 2012 | TOTAL | 41,459 | 43,053 | 84,512 | |
| YEAR | S.NO | NAME OF KEBELE | MALE | FEMALE | TOTAL |
|---|---|---|---|---|---|
| 2013 | 1 | WERABE TOWN 01+02 | 15,400 | 15,036 | 30,436 |
| 2013 | 2 | ALKESO TOWN | 1,110 | 1,101 | 2,211 |
| 2013 | 3 | ANSHOBESO | 9,671 | 10,256 | 19,928 |
| 2013 | 4 | AGEDELE ANSHOBESO | 1,144 | 1,179 | 2,323 |
| 2013 | 5 | DILEDATE | 777 | 825 | 1,603 |
| 2013 | 6 | BURAQA | 852 | 875 | 1,726 |
| 2013 | 7 | GERMAMA | 2,062 | 2,037 | 4,100 |
| 2013 | 8 | DATE WEZER 6 | 4,606 | 4,954 | 9,560 |
| 2013 | 9 | FUGIE ACHERAE | 4,801 | 5,344 | 10,145 |
| 2013 | 10 | ALBAZER | 2,631 | 2,911 | 5,542 |
| 2013 | TOTAL | 43,055 | 44,519 | 87,574 | |
| YEAR | S.NO | NAME OF KEBELE | MALE | FEMALE | TOTAL |
|---|---|---|---|---|---|
| 2014 | 1 | WERABE TOWN 01+02 | 16,108 | 15,728 | 31,836 |
| 2014 | 2 | ALKESO TOWN | 1,161 | 1,152 | 2,313 |
| 2014 | 3 | ANSHOBESO | 10,116 | 10,728 | 20,844 |
| 2014 | 4 | AGEDELE ANSHOBESO | 1,197 | 1,233 | 2,430 |
| 2014 | 5 | DILEDATE | 813 | 863 | 1,676 |
| 2014 | 6 | BURAQA | 891 | 915 | 1,806 |
| 2014 | 7 | GERMAMA | 2,157 | 2,131 | 4,288 |
| 2014 | 8 | DATE WEZER 6 | 4,818 | 5,181 | 10,000 |
| 2014 | 9 | FUGIE ACHERAE | 5,021 | 5,590 | 10,612 |
| 2014 | 10 | ALBAZER | 2,752 | 3,045 | 5,797 |
| 2014 | TOTAL | 45,035 | 46,567 | 91,602 | |
| YEAR | S.NO | NAME OF KEBELE | MALE | FEMALE | TOTAL |
|---|---|---|---|---|---|
| 2015 | 1 | WERABE TOWN 01+02 | 16,947 | 16,552 | 33,500 |
| 2015 | 2 | ALKESO TOWN | 1,281 | 1,270 | 2,551 |
| 2015 | 3 | ANSHOBESO | 10,666 | 11,306 | 21,972 |
| 2015 | 4 | AGEDELE ANSHOBESO | 1,318 | 1,355 | 2,674 |
| 2015 | 5 | DILEDATE | 916 | 968 | 1,884 |
| 2015 | 6 | BURAQA | 997 | 1,022 | 2,019 |
| 2015 | 7 | GERMAMA | 2,325 | 2,296 | 4,621 |
| 2015 | 8 | DATE WEZER 6 | 5,113 | 5,493 | 10,606 |
| 2015 | 9 | FUGIE ACHERAE | 5,326 | 5,921 | 11,248 |
| 2015 | 10 | ALBAZER | 2,948 | 3,254 | 6,202 |
| 2015 | TOTAL | 47,838 | 49,437 | 97,276 | |
| YEAR | S.NO | NAME OF KEBELE | MALE | FEMALE | TOTAL |
|---|---|---|---|---|---|
| 2016 | 1 | WERABE TOWN 01+02 | 17,760 | 17,346 | 35,408 |
| 2016 | 2 | ALKESO TOWN | 1,342 | 1,330 | 2,673 |
| 2016 | 3 | ANSHOBESO | 11,177 | 11,848 | 23,026 |
| 2016 | 4 | AGEDELE ANSHOBESO | 1,318 | 1,420 | 2,802 |
| 2016 | 5 | DILEDATE | 960 | 1,014 | 1,974 |
| 2016 | 6 | BURAQA | 997 | 1,071 | 2,114 |
| 2016 | 7 | GERMAMA | 2,325 | 2,406 | 4,842 |
| 2016 | 8 | DATE WEZER 6 | 5,358 | 5,756 | 11,115 |
| 2016 | 9 | FUGIE ACHERAE | 5,581 | 6,205 | 11,787 |
| 2016 | 10 | ALBAZER | 3,089 | 3,410 | 6,499 |
| 2016 | TOTAL | 50,011 | 51,934 | 101,945 | |
| YEAR | S.NO | NAME OF KEBELE | MALE | FEMALE | TOTAL |
|---|---|---|---|---|---|
| 2017 | 1 | WERABE TOWN 01+02 | 18,569 | 19,478 | 38,047 |
| 2017 | 2 | ALKESO TOWN | 1,336 | 1,326 | 2,662 |
| 2017 | 3 | ANSHOBESO | 11,644 | 12,348 | 23,992 |
| 2017 | 4 | AGEDELE ANSHOBESO | 1,378 | 1,420 | 2,797 |
| 2017 | 5 | DILEDATE | 936 | 994 | 1,930 |
| 2017 | 6 | BURAQA | 1,025 | 1,053 | 2,078 |
| 2017 | 7 | GERMAMA | 2,483 | 2,453 | 4,936 |
| 2017 | 8 | DATE WEZER 6 | 5,546 | 5,964 | 11,510 |
| 2017 | 9 | FUGIE ACHERAE | 5,780 | 6,434 | 12,214 |
| 2017 | 10 | ALBAZER | 3,168 | 3,504 | 6,672 |
| 2017 | TOTAL | 51,865 | 54,975 | 106,839 | |
| ዓመት / Year | ወንድ / Male | ሴት / Female | ድምር / Total | የእድገት መጠን / Growth Rate |
|---|---|---|---|---|
| 2012 | 41,459 | 43,053 | 84,512 | - |
| 2013 | 43,055 | 44,519 | 87,574 | +3.6% |
| 2014 | 45,035 | 46,567 | 91,602 | +4.6% |
| 2015 | 47,838 | 49,437 | 97,276 | +6.2% |
| 2016 | 50,011 | 51,934 | 101,945 | +4.8% |
| 2017 | 51,865 | 54,975 | 106,839 | +4.8% |
| አጠቃላይ ጭማሪ | +10,406 | +11,922 | +22,327 | +26.4% |
ምንጭ፡- በ1999 ዓ.ም የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ (ሲኤስኤ) ቆጠራ መረጃ መሰረት
የወራቤ ከተማ በብዙ የተፈጥሮ ሀብቶች የተባረከች ናት። ዋና ዋናዎቹ፡-
ዲጆ፣ ልማዛ እና ዘይወቴ ወንዞች ለግብርና፣ ለኢንዱስትሪ እና ለቤተሰብ አገልግሎት ያገለግላሉ።
ነጭ ድንጋይ፣ አሸዋ፣ ጭቃ እና ሌሎች የግንባታ ቁሳቁሶች በስፋት ይገኛሉ።
ጋፋት እና ዳጤ ወዚር 6 ተራሮች ለቱሪዝም እና ለከብት እርባታ ተስማሚ ናቸው።
ግብርና በከተማው ውስጥ ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እና የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
በከተማው ውስጥ የሚመረቱ ዋና ዋና የግብርና ምርቶች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ጤፍ፣ እንዲሁም አትክልትና ፍራፍሬ ናቸው። በ2017 ዓ.ም ዋና ዋና ሰብሎች ምርታማነት፡ በቆሎ 49 ኩ/ሄ፣ ስንዴ 42 ኩ/ሄ፣ ጤፍ 18 ኩ/ሄ።
መሰረተ ልማት ለከተማው እድገት ወሳኝ ነው። በ2017 ዓ.ም የተሟሉ ዋና ዋና አቅርቦቶች፡
24 ሰዓት የውሃ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ
የውሃ መስመር ዝርጋታ፡ 9.4 ኪ.ሜ | የጎርፍ መውረጃ ቦይ፡ 19
ዲጂታል ስልክ፣ 4ጂ፣ ኢንተርኔት አገልግሎት ይሰጣል።
በከተማው ውስጥ ስራ ፈላጊዎችን በማህበር በማደራጀት፣ ብድር በማመቻቸትና ቦታ በመስጠት የራሳቸውን ስራ እንዲፈጥሩ የማድረግ ስራ ተሰርቷል።
| ዓመት | ወንድ | ሴት | ድምር |
|---|---|---|---|
| 2015 | 2,123 | 918 | 3,041 |
| 2016 | 2,270 | 1,072 | 3,342 |
| 2017 | 3,748 | 1,967 | 5,715 |
| ጠቅላላ | 8,141 | 3,957 | 12,098 |
በወራቤ ከተማ በ2008-2015 ዓ.ም የተመዘገቡ የህብረት ስራ የመኖሪያ ማህበራት መረጃ ከዚህ በታች ቀርቧል። በአጠቃላይ 133 ማህበራት ተመዝግበዋል።
| የተላለፈበት ዓመት | የማህበር ብዛት |
|---|---|
| 2008 | 6 |
| 2009 | 12 |
| 2010 | 21 |
| 2011 | 11 |
| 2012 | 14 |
| 2013 | 25 |
| 2014 | 28 |
| 2015 | 41 |
| ድምር | 133 |
ከ2008-2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ በህብረት ስራ መኖሪያ ማህበራት የተጠቀሙ ወጣቶች፣ ሴቶች እና ሌሎች አካላት እንዲሁም የተፈጠረው የስራ እድል እና የተሰጠው የመሬት መጠን ከዚህ በታች ቀርቧል።
| የተላለፈበት ዓመት (2008-2015) | የማህበር ብዛት | ተጠቃሚ የሆኑ ወጣቶችና ሴቶች | ተጠቃሚ አካላት | የተፈጠረ ስራ ዕድል | የመሬት መጠን (ሄክታር) | ||||||
|---|---|---|---|---|---|---|---|---|---|---|---|
| ወ | ሴ | ድ | ወ | ሴ | ድ | ወ | ሴ | ድ | |||
| 2008-2015 | 133 | 420 | 790 | 1,210 | 1,106 | 790 | 1,896 | 1,945 | 2,258 | 4,203 | -- |
| ጠቅላላ / Total | 420 | 790 | 1,210 | 1,106 | 790 | 1,896 | 1,945 | 2,258 | 4,203 | -- | |
ከ2011 እስከ 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ በህብረት ስራ መኖሪያ ማህበራት የተገነቡ የቤቶች ብዛት ከዚህ በታች ቀርቧል።
| ዓመት | ብዛት |
|---|---|
| 2011 | 21 |
| 2012 | 21 |
| 2013 | 28 |
| 2014 | 33 |
| 2015 | 2 |
| ድምር | 105 |
የወራቤ ከተማ አጠቃላይ ገቢ፣ መደበኛ ገቢ እና የማዘጋጃ ቤት ገቢ ከ2012 እስከ 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ እድገት አሳይቷል።
| ምድብ | 2012 ክንውን | 2013 ክንውን | 2014 ክንውን | 2015 ክንውን | 2016 ክንውን | 2017 ክንውን | 2018 ክንውን |
|---|---|---|---|---|---|---|---|
| ጠቅላለ ገቢ ብር | 95,534,204 | 130,723,596 | 198,519,059 | 274,574,455 | 346,020,649 | 536,679,021 | 1,071,526,166 |
| መደበኛ ገቢ ብር | 50,341,352 | 73,838,124 | 119,869,599 | 175,439,699 | 213,708,965 | 324,277,053 | 734,691,515 |
| ማዘጋጃ ቤት ገቢ ብር | 45,192,852 | 56,885,471 | 78,649,459 | 99,134,756 | 132,311,684 | 212,401,968 | 336,834,651 |
የወራቤ ከተማ አጠቃላይ የፋይናንስ ሀብት በለፉት አምስት ዓመታት በአማካይ 69.7% እያደገ የመጣ ሲሆን፣ ከ255 ሚሊዮን ብር (2014) ወደ 842 ሚሊዮን ብር (2018 እቅድ) አድጓል።
| ዓመት | መደበኛ ወጪ |
|---|---|
| 2011 | 111,941,464 |
| 2012 | 136,814,991 |
| 2013 | 188,887,100.42 |
| 2014 | 264,391,895.12 |
| 2015 | 344,404,693.67 |
| ዓመት | የትሬዠሪ ድጎማ (ብር) |
|---|---|
| 2011 | 36,549,789 |
| 2012 | 36,723,060 |
| 2013 | 50,142,978 |
| 2014 | 60,185,758 |
| 2015 | 63,261,281 |
| ዓመት | የካፒታል ወጪ (ብር) |
|---|---|
| 2011 | 35,007,271 |
| 2012 | 40,556,292.19 |
| 2013 | 37,479,592 |
| 2014 | 51,862,544.9 |
| 2015 | 107,681,181 |
| የተያዘላት ዘርፍ | የታቀደ መጠን (ሄክታር) | አፈጻጸም መጠን (ሄክታር) | መቶኛ (%) |
|---|---|---|---|
| መኖሪያ | 1,887.96 | 308.02 | 16.61% |
| አስተዳደር | 314.66 | 38.58 | 2.08% |
| ንግድ እና ተጓዳኝ | 629.328 | 137.944 | 7.44% |
| ማምረቻ እና ማከማቻ | 692.252 | 127.77 | 6.89% |
| ማህበራዊ እና ማዘጋጃቤታዊ አገልግሎቶች | 1,321.572 | 287.262 | 15.49% |
| ትራንስፖርት | 1,887.96 | 488.11 | 26.33% |
| መዝናኛ እና ያልለሙ አካባቢዎች | 3,108.795 | 39.70 | 2.14% |
| ጠቅላላ | 15,733.00 | 1,853.919 | 100% |
በማውቅራዊ ፕላን የተካተተው የሰፈር ልማት ትግበራ ከግማሽ በላይ የሚሆነው መልማቱን የሰያል። በዕቅድ ከተያዘው የመሬት አጠቃቀም ለመኖሪያ 1887.96 ሄ/ር ውስጥ 308.02 ሄ/ር (16.61%)፣ ለአስተዳደር ከ314.66ሄ/ር ውስጥ 38.58ሄ/ር (2.08%)፣ ለንግድ እና ተጓዳኝ ከ629.328 ሄ/ር ውስጥ 137.944 ሄ/ር (7.44%)፣ ከማምረቻና ማከማቻ ከ692.252 ሄ/ር ውስጥ 127.77 ሄ/ር (6.89%)፣ ከማህበራዊና ማዘጋጃቤታዊ አገልግሎቶች ከ1321.572 ሄ/ር ውስጥ 287.262 ሄ/ር (15.49%)፣ ከትራንስፖርት 1887.96 ሄ/ር ውስጥ 488.11 ሄ/ር (26.33%)፣ ከመዝናኛ እና ያልለሙ አከባቢ ከ3108.795 ሄ/ር ውስጥ 39.70 ሄ/ር (2.14%) የለማ ሲሆን በአጠቃላይ ከ15,733.00 ሄ/ር ውስጥ ነባሩ ተቀናሽ ተደርጎ ሲሰላ 1853.919 ሄ/ር መልማት ተከናውኗል።
በከተማው 179 ሞንመንቶች ይገኛሉ። የካዳስተር የመሬት ምዝገበና መረጋገጥ ስራን በይፋ የተጀምረው ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ሲሆን 13,560 ህገዊ ይዞታዎች በመለያት፣ 2,780 ይዞታ በመረጋገጥ፣ 820 ይዞታዎችን የመመዝገብ ስራ ተሰርቷል።
እስከ 2014 ዓ/ም ድረስ 109,000,000 ብር፣ በ2015 በጀት ዓመት ደግሞ 40,887,993.3 ብር በድምሩ 149,887,993.3 ብር፣ 74,000,000 ከአከባቢ የተዛማጅ መዋጮ በድምሩ 223 ሚሊዮን ብር በላይ መድበን በስራ ላይ አውለናል።
በቁጥር 8 እና 4.3 ሄክታር መናፈሻዎች እና 5.2 ሄክታር የህዝብ ፓርክ ለምቶዋል።
| ዘርፍ | የተላለፈ መሬት (ሄ/ር) |
|---|---|
| አገልግሎት | 34 |
| ከተማ ግብርና | 9 |
| ኢንዱስትሪ | 176 |
| ሪል ስቴት | 21 |
| ሆቴል | 31 |
| ሎጅ | 3 |
| ንግድ | 52 |
| ተ.ቁ | ዓ.ም | መኖሪያ የቀረበ ዙር | የቀረባ ፕሎት ብዛት | ንግድ የቀረበ ዙር | የቀረበ ፕሎት ብዛት |
|---|---|---|---|---|---|
| 1 | 2012-2015 | 11 ዙር | 1,195 | 8 ዙር | 261 |
| ዓመት | ኢንዱስትሪ | መኖሪያ | ኢንቨስት | ሪል ስቴት | ለንግድ |
|---|---|---|---|---|---|
| 2011 | 15.7 | 7.3 | 5.28 | 0.5 | 2.12 |
| 2012 | 23.7 | 11 | 8.5 | 3 | 5.28 |
| 2013 | 25.05 | 15.96 | 11 | 9 | 10.54 |
| 2014 | 24.5 | 18.3 | 10.54 | 11 | 15.7 |
| 2015 | 28.54 | 18.9 | 15.7 | 15 | 19.2 |
| ተ/ቁ | የከተማው ስም | የቦታው አገልግሎት | የጨረታ ቁጥር | አማካይ ተሳታፊዎች | ከፍተኛ አሸናፊ ዋጋ (ብር) | ዝቅተኛ አሸናፊ ዋጋ (ብር) |
|---|---|---|---|---|---|---|
| 1 | ወራቤ | መኖሪያ | 14 | 5 | 4,400 | 500 |
| 2 | ወራ | መኖሪያ | 16 | 3 | 3,794 | 125 |
| 3 | ወራቤ | መኖሪያ | 17 | 3 | 2,513 | 600 |
| 4 | ወራቤ | መኖሪያ | 18 | 8 | 5,278 | 505 |
| 5 | ወራቤ | መኖሪያ | 19 | 13 | 7,529 | 540 |
| 6 | ወቤ | መኖሪያ | 20 | 3 | 2,500 | 1,551 |
| 7 | ወራቤ | መኖሪያ | 21 | 6 | 4,532 | 1,405 |
| 8 | ወራቤ | መኖሪያ | 22 | 9 | 6,500 | 2,100 |
| 9 | ወራቤ | መኖሪያ | 23 | 12 | 7,250 | 2,910 |
| 10 | ወራቤ | መኖሪያ | 24 | 16 | 7,850 | 3,720 |
| 11 | ወራቤ | መኖሪያ | 25 | 14 | 7,728 | 4,160 |
| ተ/ቁ | የከተማው ስም | የቦታው አገልግሎት | የጨረታ ቁጥር | አማካይ ተሳታፊዎች | ከፍተኛ አሸናፊ ዋጋ (ብር) | ዝቅተኛ አሸናፊ ዋጋ (ብር) |
|---|---|---|---|---|---|---|
| 12 | ወራቤ | ንግድ | 21 | 9 | 10,505 | 1,012 |
| 13 | ወራቤ | ንግድ | 22 | 7 | 8,855 | 5,000 |
| 14 | ወራቤ | ንግድ | 23 | 8 | 10,500 | 715 |
| 15 | ወራቤ | ንግድ | 24 | 8 | 10,505 | 1,012 |
| 16 | ወራቤ | ንግድ | 25 | 7 | 8,700 | 3,059 |
| 17 | ወቤ | ንግድ | 26 | 7 | 8,855 | 5,000 |
| 18 | ወራቤ | ንግድ | 27 | 5 | 7,678 | 4,305 |
| 19 | ወራ | ንግድ | 28 | 3 | 6,502 | 3,610 |
በወራቤ ከተማ የነጋዴዎች ብዛት ከ2011 እስከ 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ እድገት አሳይቷል።
| ዓመት | ደረጃ ሀ | ደረጃ ለ | ደረጃ ሐ | ድምር |
|---|---|---|---|---|
| 2011 | 182 | 78 | 993 | 1,253 |
| 2012 | 197 | 84 | 1,156 | 1,437 |
| 2013 | 211 | 97 | 1,306 | 1,614 |
| 2014 | 231 | 94 | 1,645 | 1,970 |
| 2015 | 256 | 99 | 1,994 | 2,349 |
6. ማህበራዊ ሁኔታ
ትምህርት
ትምህርት ለአንድ ሀገር እድገትና ልማት ቁልፍ መሣሪያ ነው። በወራቤ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ስር ከ2014-2017 ዓ/ም ድረስ የሚገኙ የግል እና የመንግስት ት/ት ቤቶች እንደሚከተለው ናቸው።
የትምህርት ቤቶች እድገት / School Growth
የተማሪዎች ስርጭት በፆታ (2017) / Student Distribution by Sex
የመንግስት እና የግል ት/ት ቤቶች ብዛት (2014-2017 ዓ.ም)
በመንግስት ት/ት ቤት የሴክሽን ብዛት በክፍል ደረጃ (1-8)
በመንግስት ት/ት ቤት የሴክሽን ብዛት በክፍል ደረጃ (9-12)
በግል ት/ት ቤት የሴክሽን ብዛት በክፍል ደረጃ
2017 በዓመቱ ለመማር የተመዘገቡ ተማሪዎች ብዛት መረጃ (መንግስት ት/ት ቤት)
2017 በማታው የት/ት ፕሮግራም የተመዘገቡ ተማሪዎች ብዛት
2017 በግል ት/ት ቤት የተመዘገቡ ተማሪዎች ብዛት
ጥምርታዎች
ጤና
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራቸው ካሉ ስራዎች አንዱ የጤና ልማት ስራ ነው። ከተማ አስተዳደሩ ሲመሰረት አንድ የማህበረሰብ ክሊኒክ የነበረ ሲሆን እያደገ የመጣውን የማህበረሰቡን የጤና ፍላጎት መነሻ በማድረግ የጤና ተቋማት ተደራሽነት በማሳደግ ረገድ ሰፊ ስራዎች ተሰርተዋል።
የጤና ተቋማት እድገት / Health Facilities Growth
የጤና ባለሙያዎች ስርጭት / Health Professionals Distribution
የጤና ተቋማት መረጃ (2015-2017 ዓ.ም)
የዲግሪ ባለሙያዎች ብዛት (2017 ዓ.ም)
የዲፕሎማ ባለሙያዎች ብዛት (2017 ዓ.ም)
የላቦራቶሪ እና መድሀኒት ቤቶች መረጃ
የጤና አገልግሎት መረጃ (2017 ዓ.ም)
የእናቶች ጤና አገልግሎት መረጃ
የህጻናት ጤና እና አልምነት መረጃ
የክትባት አገልግሎት መረጃ
የኤች አይ ቪ መከላከል አገልግሎት መረጃ (2017)
የአካል ጉዳተኞች ብዛት በአይነት
ቱሪዝም
ወራቤ ብዙ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህቦች አሏት፡
አልከሶ መስጊድ
አልከሶ መስጊድ በወራቤ ከተማ ውስጥ ከሚገኙት የቱሪስት መስህብ ቦታዎች አንድ እና ዋነኛው ሲሆን ከማይንቀሳቀሱ ቅርሶች ውስጥ ይመደባል፡፡ አልከስዬ እ.ኢ.አ 1858 ዓ.ም እንዶፎ በሚባል ደጋማ አከባቢ ተወለዱ፡፡ እ.ኢ.አ 1935 በ77 አመታቸው የአልከሶን መስጊድ ለመገንባት ሲያስቡ 360 በላይ የጽድ ፍልጦችን አምጥተዋል።
ዘፎ ፏፏቴ
33 ሜትር ቁመት ያለው ተፈጥሯዊ ፏፏቴ ሲሆን ከማይንቀሳቀስ ቅርስ ይመደባል፡፡ ፏፏቴው ወርዶ የሚያርፍበት ትንሽ ወንዝ ጥልቀቱ 12 ሜትር በላይ እንደሆነ ይገመታል። የከተማው ነዋሪዎች ለመዋኘትና ፎቶ ግራፍ ለመስራት ይመጣሉ።
ገንቦ ዋሻ
በወራቤ ከተማ 01 ቀበሌ የሚገኘው የገንቦ ዋሻ በገሜ ጎጥ በዘይወት ወንዝ በስተ ምስራቅ ይገኛል። አንድ ትልቅ መግቢያ ያለው ሲሆን ወደ ውስጥ ሲገባ በሁለት የተከፈሉ መንገዶች አሉት። ሁለት መግቢያ ያለው ተፈጥሯዊ ዋሻ ነው።
ጉንዳ ተፈጥሯዊ ድልድይ
የጉንዳ ድልድይ ከተፈጥሮ የመስህብ ቦታዎች ሲመደብ ከማይንቀሳቀሱ ቅርሶች ውስጥ አንዱ ነው። በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ ከዋናው መንገድ 22 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል። የተፈጥሮአዊ ድልድይ ስፋቱ 1 ሜትር ሲሆን የክብ ቀዳዳው ስፋት 3 ሜትር ነው። ጥልቀቱ 7 ሜትር ያህል ነው።
የጉድሮ ደን
የጉድሮ ተፈጥሯዊ ደን በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ በዳጤ ወዘር 6 ቀበሌ ከከተማው ከዋናው መንገድ በስተሰሜን 11 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል። በደኑ ውስጥ ጅብ፣ ቀበሮ፣ ሚዳቆ፣ ጥንቸል፣ ዠግራ እና ቆቅ ይገኛሉ።
የስልጤ ባህላዊ መገልገያ ቁሳቁሶች
የስልጤ ብሔረሰብ የበለጸገ ባህላዊ ቅርስ አለው። የተለያዩ ባህላዊ መገልገያ ቁሳቁሶች በወራቤ ከተማ ይገኛሉ። እነዚህ ቅርሶች የስልጤ ህዝብ ባህላዊ ማንነት የሚያንጸባርቁ ናቸው።